Monday, December 05, 2016

ከአዲስ አበባ 100 ኪሜ ርቀት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

ከአዲስ አበባ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ 100 ኪሜ ርቀት በደብረ ብርሃን ምስራቃዊ ዳርቻ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሌሊት 10:55 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ፡፡ የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል ከአራት ነጥብ አምስት በመቶ በላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡

የመሬት መንቀጥቀጡ አዲስ አበባ ከተማ ጀሞ አካባቢ መሰማቱም ታውቋል፡፡ ባልደረባችን ዩሃንስ ፍሰሀ  በዚህ ዙሪያ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና የአስትሮኖሚ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር እንዲሁም የመሬት መንቀጥቀጥ ባለሙያ የሆኑትን ዶክተር አታላይ አየለን በስልክ አነጋግሯቸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment