Friday, May 03, 2013

የእነአቶ አንዱዓለም ይግባኝ ውድቅ ተደረገ

(ዓርብ, ሜይ 03, 2013))--በአሸባሪነትና በአገር ክህደት ወንጀል ተከስሰው በተፈረደባቸው በአቶ አንዱ ዓለም አራጌ፣ በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በአቶ ናትናኤል መኮንንና በሌሎችም ላይ የበታች ፍርድ ቤት ቀደም ሲል ያሣለፈውን ፍርድ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አፀና።



የእነ አቶ አንዱዓለም አራጌ ጠበቆች ደምበኞቻቸው ከፈቀዱ ጉዳዮን ወደ ሰበር ችሎት ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል ።

በምኅፃር ሲፒጄ የሚባለው የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋች ዓለምአቀፍ ድርጅት - Committee to Protect Journalists የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባሣለፈው ውሣኔ ላይ፣ በተለይ ስለ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባወጣው መግለጫ “… ፖለቲካዊ ፍርድ ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ያላትን ገጽታ ያዋርዳል …” ብሏል። “ፍርዱ በጣም አሳሳቢ የሆነው በአሸባሪነት ወንጀል ላይ የሚቀልድ በመሆኑ ነው” ብሏል ድርጅቱ በመግለጫው አክሎ። Read more from Voice of America »

No comments:

Post a Comment